News & Products

Awareness creation on Industrial Input policy and strategy was given
11/03/2025

Financial and Audit Report 2020/21
28/01/2025

Financial and Audit Report
25/10/2023

Top management of Ethiopian Investment Holdings held a discussion and working visit with the management of EIIDE
26/12/2024

Managers and Employees of EIIDE visited the new head office under construction
02/12/2024

EIIDE secured 1.94 Billion Birr on the four months of the fiscal year
23/10/2024

Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise and Ethiopian Post signed a memorandum of understanding
23/10/2024

A discussion was held on the challenges and solutions of the supply of industrial inputs
14/10/2024

Congratulations !!
11/10/2024

EIIDE awarded its management and employees for the successful performance of the 2023/24 fiscal year
26/08/2024

EIIDE became the highest awardee of the Abyssinian Industrial Award
22/07/2024

Managers and employees of the Public Enterprises Holding and Administration and responsible institutions conducted sapling planting
20/07/2024

EIIDE conducted Ten-month plan implementation and 2024/25 corporate plan review of central and western districts
20/05/2024

EIIDE Reviewed it's Strategic Plan and other operating manuals
13/05/2024

EIIDE is Reviewing it's Strategic Plan and other operating manuals
10/05/2024

EIIDE participated in 'Ethiopia Tamrt' Expo
09/05/2024

EIIDE participated in the 10th International Cooperatives Exhibition and Bazaar
15/02/2024

Members of the Standing Committee on Trade and Industry of the House of peoples Representatives visited EIIDE
29/01/2024

EIIDE conducted Six month Plan performance Evaluation
17/01/2024

Sales Announcement
27/11/2023
በግብዓት አቅርቦት ፓሊሲ፣ ስትራቴጅዎች እና ሌሎች ሰነዶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት(ኢኢግልድ) ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት በኢንዱስትሪ ግብዓቶች አቅርቦት ጋር በተያያዘ የአምራች ኢንዱሰትሪውን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በተዘጋጀ ፖሊሲ፣ በተቀረፁ የተለያዩ ጥናቶችና ስትራቴጂዎች ላይ ከየካቲት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት በቢሾፍቱ ከተማ ለኢኢግልድ ከፍተኛ አመራሮች፣ ከተለያየ ክፍል ለተውጣጡ ዳይሬክተሮች፣ የዲሰተሪክት ሃላፊዎችና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡
በስልጠናው የኢኢግልድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ስልጠናውን ያስጀመሩ ሲሆን የስልጠናው ዋና ዓላማ ኢኢግልድ ከኢንዱስትሪዎች ፍላጎት አንጻር የግብዓት አቅርቦት ስራ ሂደቱን ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ስትራቴጂ ጋር የተናበበና የተቀናጀ በማድረግ ለመስራት እና የግብዓት አቅርቦት ሰንሰለቱን የተሳለጠ በማድረግ በቀጣይ ውጤታማ ስራ ለመስራት እንዲያስቻል ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን አመልክተዋል፡፡
ለሁለት ቀናት በተካሄደው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና የተለያዩ ስትራቴጂዎችና ጥናቶች የቀረቡ ሲሆን የኢትዮጲያ የኢንዱስትሪ ፖሊሲ፣ የተኪ ምርት ስትራቴጂ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ የትስስር ስትራቴጅ ሰነድ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የኤክስፖርት ስትራቴጂ፣ የቆዳ ስትራቴጂና የማስፈጸሚያ ስልት እንዲሁም የጥጥ ግብይት ስርዓት ጥናቶች ለስልጠናው ተሳታፊዎች ቀርበዋል፡፡ በቀረቡት ሰነድ ላይም የስልጠናው ተሳታፊዎች ከኢኢግልድ አንፃር ጥያቄዎችን እና አስተያየቶችን በማቅረብ ሰፋ ያለ ውይይት በኢንዱሰትሪ ሚኒሰቴር የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ዋና ዳይሬክተር በሆኑት ዶ/ር ሚልኬሳ ጃግሜ እና በአሰልጣኞች አወያይነት ተካሂዷል፡፡
በመጨረሻም የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሚልኬሳ ጃግሜ በስልጠናውና የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐግብር ማጠናቀቂያ ላይ እንደገለጹት የዚህ ዓይነት የስልጠና መድረክ በኢንዱስትሪ ግብዓት አቅርቦት ዘርፍ ዋና ባለድርሻ ለሆኑት የኢኢግልድ ከፍተኛ፣ መካከለኛ አመራሮችና ባለሙያዎች መዘጋጀቱ የኢንዱስትሪ ግብዓት አቅርቦት ሰንሰለቱን የተሳለጠ እንደሚያደርገው አመልክተው፤ የዚህ ዓይነት ይዘት ያላቸው የተለያዩ ነገር ግን የአንድ ዓላማ ግብን ለማሳከት የሚያስችሉ፤ ተቋማትን የሚያስተሳስሩ ስትራቴጂዎችና ጥናቶች ላይ የጋራ ግንዛቤ መያዝ በእጅጉ አስፈላጊ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል፡፡