ለሻሸመኔ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በደረጃ 7 የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ
06/30/2026
- 07/03/2026 |

                                                                 

                                    

ቀን፡- ሰኔ 22/2018 ዓ.ም

ለሻሸመኔ ደረጃ አንድ ቅ/ጽ/ቤት በደረጃ 7 የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ የሥራ መደብ በውጭ ቅጥር ለማሟላት በወጣው ማስታወቂያ የጽሑፍ ፈተና የወሰዱ ተወዳዳሪዎች ውጤት መግለጫ

ድርጅታችን ለሻሸመኔ ደረጃ አንድ ቅ/ጽ/ቤት በደረጃ 7 የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ

አንድ ክፍት የሥራ መደብ በዝውውርና በእድገት ማግኘት ባለመቻሉ በሪፖርተር

ጋዜጣ ግንቦት 16/2018 ዓ.ም. በወጣው የውጭ ቅጥር ማስታወቂያ መሠረት

ተወዳዳሪዎች የጽሑፍ ፈተና የወሰዱ ተወዳዳሪዎች ያገኙት ውጤት እንደሚከተለው

የተገለጸ ሲሆን፣ የቃለ መጠይቅ ፈተና የሚሰጠው ሐሙስ ሰኔ 25/2018 ዓ.ም

ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ስለሆነ በሰው ኃብት አስተዳደር ቡድን ቢሮ እንድትገኙ

እያሳሰብን፣ በውድድሩ ቅሬታ ያላችሁ አመልካቾች ማስታወቂያው ከወጣበት

ቀን ጀምሮ እስከ 3 ቀን ድረስ ለሰው ኃብት ሥራ አመራር ዳይሬክቶሬት

እንድታቀርቡ እናሳስባለን፡፡ 

ለውድድር የቀረቡ አመልካቾች፡-

ተ. ቁ

የአመልካቾች ሙሉ ስም

የጽሑፍ ፈተና ውጤት ከ70%

መሠረት አየነው ቁምሌ

49

ጫላ ታዬ ዋቅጅራ

49

 

  

                                            ድርጅቱ

Apply For Tender Document