የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት ብር 265 ሚሊዮን የተጣራ ትርፍ ማግኘቱ ተገለጸ
EIIDE Reviewed it's Strategic Plan and other operating manuals
13/05/2024
EIIDE is Reviewing it's Strategic Plan and other operating manuals
10/05/2024
EIIDE participated in 'Ethiopia Tamrt' Expo
09/05/2024
EIIDE participated in the 10th International Cooperatives Exhibition and Bazaar
15/02/2024
Members of the Standing Committee on Trade and Industry of the House of peoples Representatives visited EIIDE
29/01/2024
EIIDE conducted Six month Plan performance Evaluation
17/01/2024
Sales Announcement
27/11/2023
Announcement regarding the supply of premix needed to enrich cooking oil with vitamins
06/11/2023
EIIDE evaluates its first quarter plan performance at Elilly Hotel
06/11/2023
Notice
25/10/2023
EIIDE donated 4.2 million birr sanitary pad
17/10/2023
EIIDE offered 16.5 million liters of edible oil at a reasonable price
14/09/2023
EIIDE conducted an evaluation of the of the 2022/23 fiscal year plan and the next year's plan of the enterprise
23/08/2023
Members of the Management Board visited projects of EIIDE
31/07/2023
Managers and Employees of EIIDE Conducted Green Legacy
27/07/2023
EIIDE has launched a women's workers forum
20/07/2023
ኢኢግልድ የ2015 በጀት ዓመት የስምንት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ
11/04/2023
ኢኢግልድ ለ33 የድርጅቱ ባለሙያዎች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ልማትና ትግበራ ስልጠና ሠጠ
23/03/2023
ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ ፕሮጀክቶች ግንባታ ገብኝት ተካሄደ
18/01/2023
አርአያነት ያለው ተግባር
14/09/2022
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በ2014 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 6 ወራት አፈጻጸም ብር 265 ሚሊዮን የተጣራ ትርፍ ማግኘቱ ተገለጸ፡፡
ይህ የተገለጸው ድርጅቱ የ2014 በጀት ዓመት የስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸሙንና የቀጣዩን ስድስት ወራት ዕቅድ የድርጅቱ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ እና አባላት፣ የድርጅቱ የበላይና መካከለኛ አመራሮችና የድርጅቱ ሠራተኞች በተገኙበት ጥር 28 እና 29 / 2014 ዓ.ም በቢሾፍቱ ባዘጋጀው የግምገማና የምክክር መድረክ ላይ ነው፡፡
በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የድርጅቱ ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ተካ ገ/የስ እንደገለጹት ድርጅቱ ከነበረበት አሰከፊ ችግሮች ወጥቶ የሪፎርም ሥራዎችን በማከናወን ለትርፋማነት መድረሱ፤ የድርጅቱ ሠራተኞችና አመራሮች ጥምር ውጤት ሲሆን ይህንን ውጤት አጠናክሮ በመቀጠል ኢኢግልድ በቀጣይም የተሸለ ውጤት ለማስመዝገብ በቁርጠኝነት መስራት ይገባል፡፡
አያይዘውም በድርጅቱ የተሻለ አደረጃጀትና የአሰራር ሥርዓት ለመዘርጋት ከተደረገው የእስካሁኑ ጥረት በተጨማሪ በቀጣይም ጊዜያት የተጀመረሩትን የሪፎርም ሥራዎች በማጠናከር ወደላቀ ደረጃ ከፍ ለማድረግ የአመራሩና የሰራተኞች ተቀነቀጅቶ መስራት ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ እንደገለጹት የድርጅቱ አመራሮችና የዲስትሪክትና የሽያጭ ቅርንጫፍ ሃላፊዎች ድርጅቱን ወደተሸለ ደረጃ ለማሻገር የተጀመሩትን የሪፎርም ስራዎች በማስቀጠል በተጠናከረ መንገድ ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ለመግባት ከወዲሁ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል፡፡
አያይዘውም የድርጅቱ የበላይ አመራር የአሰራር ክፍተቶችን በመሙላት ድርጅቱን ወደተሻለ ደረጃ የሚያሻግር አሰራሮን የመተግበር ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክተዋል፡፡
ለሁለት ቀናት በተካሄደው በዚሁ የግምገማና የምክክር መድረክ የድርጅቱ የ2014 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት አፈጻጸም ሪፖርትና የቀሪዎቹ ስድስት ወራት እቅድ በስትራቴጂክ እቅድ ዝግጅትና ግምገማ ዳይሩክቶሬት ቀርቦ በጥልቀት ግምገማና ውይይት ተካሂዶበታል፡፡